በሆሳዕና ከተማ የቃለ ሕይወት አጥቢያዎች ሕብረት በቀን 2/3/2011 ዓ/ም ከ15 አጥቢያ ለመጡ ወ = 13 ሴ = 13 ድ = 26 የቤተሰብ መሪዎች (ባልና ሚስት) መጋቢያንና ወንጌላዊን ቤተሰብ አድን አገልግሎት ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፡፡
በስልጠናዉ ወቅት የተሳተፉ ሰልጣኞች የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ መምጫ በደጅ በሆነ ሰዓት ቤተሰብን ለእግዚአብሔር መንግሥት ለማዘጋጀት እንድንችል ስልጠናዉ መነቃቃትን የፈጠረ፣ ሌሎችንም በአጥቢያ የሚገኙ ትን የቤተሰብ መሪዎችን ለማስተማር እና ለማሰልጠን ግንዛቤ አግኝተናል ብለዋል፡፡ አለም አቀፍ ቤተሰብ አድን አገልግሎት ቤተሰብን በሚመለከት ስላለዉ ራዕይ እግዚአብሔርን በማመስገን በጎናችሁ ነን ብለዉ አገልግሎቱን አበረታተዋል፡፡