Wolaita Sodo, Ethiopia
info@isfministry.org
+251936339292
Save the Family, Save the Church
 

By faith Noah, being warned of God of things not seen as yet, moved with fear, prepared an ark to the saving of his house; Hebrew 11:7

ቤተሰብ አድን አገልግሎት አንደኛ መጽሐፍ ጥናት ያጠናቀቁ ባለትዳሮች ምረቃ ተካህዷል
ቤተሰብ አድን አገልግሎት አንደኛ መጽሐፍ ጥናት ያጠናቀቁ ባለትዳሮች ምረቃ ተካህዷል

በቦዲቲ ዕድገት ቃለ ሕይወት ቤ/ያን ቤተሰብ አድን አገልግሎት መጽሐፍን ለ3 ወራት አጥንተዉ የጨረሱ 22 የቤተሰብ መሪዎች የካቲት 15/2016 ተመረቁ፡፡ በአለም አቀፍ ቤተሰብ አድን አገልግሎት ስልጥነዉ የሚያሠልጥኑ (ቲኦቲ) የቤተክርስቲያን ሰልጣኞች መካከል በቦዲቲ ከተማ ዕድገት ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የቤተሰብ አድን አገልለሎት ቤተሰብን ደቀ መዝሙር ማድረግ ዘዴና ትምህርቶቹ አንደኛ መጽሐፍ ለ3 ወር አጥንተዉ የጨረሱት ባለትዳሮች እሁድ ባለዉ አምልኮ ፕሮግራም ለሌሎች ትምህርት በሚሆን መልክ የአለም አቀፍ ቤተሰብ አድን አገልግሎት ቦርድ አባላት በተገኙበት በሠርትፍኬት ተመርቀዋል፡፡ ሰልጣኞች በጥናቱ ስለ ቤተሰብ ግንዛቤ የፈጠሩና ቤተሰቦቻቸዉን ለእግዚአብሔር መንግስት ለማዘጋጀት የሚያስችል ትምህርት እንዳገኙ የገለጹ ሲሆን ፤ የቤተክርስቲያን መሪዎችም ያጠኑ አባላት ሌሎችን ማሰልጠን የሚችሉ በመሆናቸዉ ለቤተክርስቲያን ጠቃሚ ስለሆነ እንደሚያስቀጥሉ ተናግረዋል፡፡   

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *